በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን
ጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
የበርሊን ደብረ ገነት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስትያን

Äthiopisch-Orthodoxe Tewahido Kirchengeminde in Deutschland
Debre-Genet Sankt Immanuel zu Berlin

Gottesdienste

Taufe

ክርስትና

እንዲህም አላቸው። ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።

የማርቆስ ወንጌል ፲፮ ፥፲፭ – ፲፮

Geistige Verbindung

ሥርዓተ ተክሊል

ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፥ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ። ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም።

የማቴዎስ ወንጌል ፲፱ ፥ ፭ – ፮

Heilige Kommunion

ቅዱስ ቁርባን

የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው።

የዮሐንስ ወንጌል ፮፥ ፶፫ -፶፬ 

Gebet für die Toten

ጸሎተ ፍትሐት

አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።።

፩ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ፲፭፥ ፳

Qomos Aba Abraham

መልአከ ገነት ቆሞስ አባ አብርሃም ገ/ሚካኤል

የደብሩ አስተዳዳሪ

“ምሕረኒ እግዚኦ ፍኖተ ጽድቅከ፣ወእኅሥሣ በኩሉ ጊዜ”
“አቤቱ የእውነትህን መንገድ አስተምረኝ፣ ሁልጊዜም እፈልጋታለሁ።” መዝ 118-30

ይኽንን በይነ መረብ ለምታዩልን አባቶቻችንና ምዕመናን ወምዕመናት ሁሉ እንኳን ወደ እኛ ዝግጅት መጣችሁልን በሚል ልጀምረውና መቼም እንደምታውቁት በዛሬ ጊዜ ልማር ላለና በአንሰሃስሆ መንፈስ ቅዱስ ለተነቃቃ ሁሉ መምህራኑ ወደ ነበሩበት የርቀት ዘመንና ቦታ መሄድ ሳያስፈልገው እነርሱ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ በሰጠው ጥበብ/Technology/አማካኝነት በድምጽና በጽሁፋቸው እኛ ወዳለንበት ጊዜና ቦታ እየመጡ ስለሆነ ከስንፍና እና ከድካም በቀር የመምሕራንና የትምህርት ችግር በተለይም እንደልብ የቴክኖሎጂው ፍሰት ባለባቸው አህጉራት ለምንኖረው ምክንያት አይሆነንም!!

በመጽሐፈ ፊልክስስዮስ ላይ ከተፃፈው የአበው ታሪክ ውስጥ አባታችን ታላቁ መቃርስ በአንድ ወቅት አንድ ሴት ወደ እርሱ ዘንድ ለቡራኬ መጥታ በጥልቀት ወደ እርሱ ስትመለከት አፍሮ አንገቱን ሰበር አድርጎ መሬት መሬት ማየት ጀመረ ይለናል። ሴትዮይቱ አባታችን ስለምን ምክንያት ወደ መሬት ታያለህ?ብትለው እርሱም መልሶ አንቺስ ስለምን እንዲህ አድርገሽ ወደ እኔ ትመለከቻለሽ? በማለት እንዳጎነበሰ ጥያቄዋን በጥያቄ መለሰላት።  እርሷም እንዲህ አለችው  ፟ሴት ከወንድ ተፈጥራለችና እኔ ወደ አንተ አየሁ!አንተ ከአፈር ተፈጥረሃልና መሬት መሬት አየህ!  አለችው ይኽም አባት ከዚህች ተራ ምዕመን ያገኘውን ትምህርት በዘመኑ ከሚያውቃቸው መምሕራን ይልቅ ቁም ነገሩን ልቆ ስላገኘው በኖረበት ዘመን ሁሉ መሬት መሬት እያየ መሄድን *አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ* ከሚለው ለአባታችን አዳም ከተነገረው ጥቅስ ጋር አመሳስሎ ለትህትናና ለእዝናት የሕይወቱ መመሪያ አድርጎት ኖሯል ይለናል። 

መቼም ካስተዋልንና ካልናቅን ብዙ ነገር ባነበብንና ባወቅን ቁጥር ለራሳችን ረብ የሚሆን ጥሩ ነገሮችን እናከማቻለን። ጽሁፎች ታላላቅ መመህራን ያስተማሩባቸው የማይታጠፉ ጉባኤያት ናቸው። ካነበብን እንማራለን ለንስሃም እንነሳሳለን።በአብዛኛው ማየት ላይ የተመረኮዙ ልምዶቻችንን ወደ ንባብ ፋታ ውስጥ ብናስገባቸው በሌላ እይታ ውስጥ ያሉትን ቁልፍ ምስጢሮች ለአእምሮአችን መመገብ እንችላለን።

የኛ ዝግጅት በደብራችን ዙሪያ ላሉ ምዕመናን ያሉንን ለማካፈል የጀመርናት እንደመሆኗ በታላላቅ ልሙዳን ከሚመሩት ጋር አትወዳደርም ነገር ግን ያለ ውልደት ልደት ያለ ልደትም ዕድገት የለም እና በውስጡ ለተሳታፊዎች በሚኖረው መድረክ ለአዘጋጆቹ የምታበረክቱት ካላችሁ ቤታችሁ ነው እነሆ *ዚአየ ለዚአከ ዚአከ ለዚአየ* እያልን የእግዚአብሔርን ቃል እንማማር እላለሁ።

Über Uns

Ziele
"Du sollst deinen nächsten lieben wie dich selbst" Levitikus 19 : 18

* Förderung der religiösen, kulturelle und sozialen Lebens ihrer Mitglieder.
* Gründung bzw. Einrichtung von Kirchen & sozialen Einrichtung.
* Psychosoziale Betreuung der Alten, Kranken und Bedürftigen.
* Förderung der Idäntität und Integration ihrer Mitglieder.

ህጻናት በቤተ ክርስትያን

“እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሉከ ስብሐተ”

“ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ”

መዝሙረ ዳዊት ፰ ፥ ፩ – ፫

ሥርዓተ ቅዳሴ

“አሀዱ አብ ቅዱስ

አሀዱ ወልድ ቅዱስ

አሀዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ”

ጸሎት

“ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ”

የማቴዎስ ወንጌል 26 ፥ 41

በደብሩ የተካሄዱ መርሐ ግብራትና በዓላት ፎቶዎች

ቪዲዮዎች

በደብራችን የተካሄዱ የተለያዩ መርሐ ግብራት (ስብከቶች፥ መዝሙራት፥ በዓላት)

Play Video

Kirchliche Vision

Unsere Vision

Was wäre Religion ohne Visionen?

Die Feindschaft der Menschen überwinden

Liebe & Glaube an die Menschen weitergeben.

Was Wir Machen?

Beten ist Gemeinschaft. Auch wenn du ganz allein auf einem Felsen betest – zur gleichen Zeit beten unzählige Menschen auf der ganzen Welt. Habe auch den Mut, mit Freunden gemeinsam zu beten. Beten verbindet und schafft Vertrauen.

Unsere Geminde

Wir glauben an Gott, den Vater, den Allmächtigen, den Schöpfer des Himmels und der Erde, und an Jesus Christus, seinen eingeborenen Sohn, unsern Herrn, empfangen durch den Heiligen Geist, geboren von der Jungfrau Maria, gelitten unter Pontius Pilatus, gekreuzigt, gestorben und begraben, hinabgestiegen in das Reich des Todes, am dritten Tage auferstanden von den Toten, aufgefahren in den Himmel;

Sonntagsgottesdienst

Unsere Gottesdienste dauern zwischen 90 und 120 Minuten. Sie starten mit einer Anbetungszeit, geleitet durch eine äthiopisch-orthodoxie Kirchen ceromonies. Dabei singen wir Gott zeitgemässe Loblieder. Die Texte werden auf Leinwände projiziert, so dass jeder ein Teil des Geschehens sein kann. In der folgenden Predigt wird ein Thema vertieft, das für ein Leben mit GOTT relevant ist. Du wirst feststellen, dass der Gottesdienst dein Leben berührt!

Nach dem Gottesdienst lädt die Cafeteria zu einem Kaffee oder einem Snack ein.

የዘወትር አገልግሎት ጊዜያት

እሁድ ከ6:00 - 10:30

የወርሃዊ አገልግሎት ጊዜያት

በሚከተሉት ቀናት እንዲሁም የዓመት ክብረ በዓላት ዕለት የሰርክ ጸሎት ከ18 ሰዓት ጀምሮ

የቅዱስ ሚካኤል (በ፲፪)
የቅዱስ ገብርኤል (በ፲፱)
የቅድስት ማርያም (በ፳፩)
የቅዱስ መድኃኔዓለም (በ፳፯)
የቅዱስ አማኑኤል (በ፳፰)
የቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ (በ፳፱)

የባቡርና የአውቶቡስ ጥቆማ

U6 Alt-Mariendorf dann mit dem Bus Nr. 181 Richtung U Walther-Schreiber-Platz,
Haltestelle: Halbauer Weg

oder

S25/S26 S Teltow Stadt dann mit dem Bus Nr. 181 Richtung Britz, Kielingerstr. oder Bus Nr. 187 Richtung Halbauer Weg,
Haltestelle: Halbauer Weg

አድራሻ

Halbauer Weg 15, 12247 Berlin
Phone: +49 176 849 275 62
Email: eotc.berlin1@gmail.com

Bank Konto (1)

Äthiopisch-Orthodoxe Kirchengemeinde St. Immanuel Berlin & Brandenburg

IBAN DE07370601936002686013

BIC   GENODED1PAX

Bank Konto (2)

Kirchenbauverein Kidus Amanuel zu Berlin e.V.

IBAN DE30370601936004900012

BIC  GENODED 1 Pax

© በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት 

የበርሊን ደብረ ገነት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስትያን | 2012 ዓ.ም.